Pages

Wednesday, May 30, 2018

አንዳርጋቸው ጽጌን በጨረፍታ

Endalegeta Kebede

.አንዳርጋቸው ጽጌ ተፈታ፤እሰይ! በኢትዮጵያ ምድር የበቀለ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሲናፍቀው የነበረ ዜና ነበርና የእሱ መፈታት ለፍትህ ለርትዕና ለሀገር ሲቆረቆሩ ለቆዩና መቆርቆር ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንና አፍቃሬ ኢትዮጵያውያን መልካም የምስራች ነው፡፡ አንዳርጋቸው የማይሰፈር ዋጋ ከፍሏል፡፡አይተናል፤ሰምተናል፡፡ የመፈታቱ ዜና በህይወት ላላሉት ተቃዋሚዎቹ/አሳሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ለሞቱትም አስደንጋጭ መርዶ ሊሆንባቸው እንደሚችል ሲገመት የቆየ ነው፡፡ እንግልቱ ደግሞ በውስን ዓመታት ብቻ የሚመደብ አይደለም፡፡ ከሃያ አምስት ዓመታት በላይ በኢህአዴግ ሲወገዝ፣ አሳዳጆቹ መቆሚያ መቀመጫ ሲያሣጡት የነበረ ሰው ነው፡፡ በደርግ ዘመንም አንዲሁ፡፡
አንዳርጋቸው ጽጌን ሳስበው ‹ነጻነት› የሚለው ቃል ብሄራዊ መዝሙር ሆኖ ወደ ጆሮዬ ይገባል፡፡ አንዳንዴ ‹ነጻነት› በሚል ርዕስ የሚታወቅ፣ሁላችንም ተቀባብለን ልንዘምረው የምንመኘው ተወዳጅና ዘመን አይሽሬ ነጠላ ዜማ ያለው ሁሉ ይመስለኛል፡፡ነጻነትን በቅጡ ሳያውቁ ነጻ እናወጣለን ስለሚሉ ታጋዮች ስለጻፈ ፣እሱም ለነጻነት በሚከፈል መስዋዕትነት ከመሪ ተዋንያን መካከል አንዱ ስለሆነ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡አሁን ተፈታ! አሁንም ምስጋና ለእነ አቢይ አህመድ(ዶክተር)ይሁን!
አንዳርጋቸው የአዲስ አበባ ልጅ ነው - አዲስ አበቤ፡፡ ከአዲስ አበባ የወጣው በ1972 ነው - በወርሃ ጥር፡፡

Tuesday, May 29, 2018

ሱስ ያደበዘዛቸው የሕይወት መስመሮች


በአፍሪካ ትልቁ ገበያ እንደሆነ በሚነገርለት በመርካቶ እንኳንስ ነጋዴው ተላልኮ የሚኖረው ምስኪን እንኳ ገንዘብ አይቸግረውም፡፡ ሌላው ቢቀር የዕለት ጉርስ ጉዳይ አያሳስበውም፡፡ የወላጆቹን የንግድ ሥራ ድርጅት ገና በልጅነቱ ለተቀላቀለው ለካሳሁን ኪሮስ ዓይነቱ ደግሞ ገንዘብ ቁም ነገሩ አይሆንም፡፡ ‹‹ብዙ ገንዘብ አገኝ ነበር፡፡ ማግኘቴን እንጂ ቆጥሬም አላውቅም፤›› ይላል ገና በ12 ዓመቱ የመርካቶን ፈጣን የንግድ እንቅስቃሴ የተቀላቀለበትን ደጉን ጊዜ ሲያስታውስ፡፡
     በንግዱም ብቻ ሳይሆን በትምህርቱም ብርቱ የነበረው ኪሮስ የስምንተኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና ላይ 95 ነጥብ አስመዝግቦ ነበር ወደ ዘጠነኛ ክፍል የተዘዋወረው፡፡ በዚህ ግን ሊቀጥል አልቻለም፡፡ እንደ ልቡ የሚያገኘው ገንዘብ ከጉርምስና ጋር ተደምሮ ማንኛውንም ነገር እንዲሞክር በሕይወቱ አላስፈላጊ ቁማር እንዲጫወት መንገድ ከፈተለት፡፡ ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ የማይወጣው ተራራ የማይወርደው ቁልቁለት አልነበረም፡፡ አደገኛ የሚባሉ ሱሶችን በተለይም መጠጥና ጫትን ይሞክርም ጀመረ፡፡

የፖለቲካ ለውጡ የፈነጠቀው ተስፋ ይኖር ይሆን?


አለማየሁ አንበሴ

• ጠ/ሚኒስትሩ የሚያነሷቸው ሀሳቦች ለሃገራዊ መግባባት ጠቃሚ ናቸው
• ሥር ነቀል የምርጫ መዋቅራዊና አስተዳደራዊ ለውጥ ያስፈልጋል
• በቅድመ ሁኔታ ላይ የታጠረ ድርድር አያስፈልግም


   የአገሪቱ የፖለቲካ ድባብ እየተለወጠ ይመስላል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞች ተፈተዋል፡፡ አሁንም እየተፈቱ ነው፡፡ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የጠ/ሚኒስትርነት መንበሩን ከያዙ ወዲህ መንግስት የተቃዋሚ ፖለቲካ ሃይሎችን የሚመለከትበት መነጽር በእርግጥም ተለውጧል፡፡ በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ለሚንቀሳቀሱት ምቹ ምህዳር ለመፍጠር መንግስት ቁርጠኝነቱ እንዳለው ጠ/ሚኒስትሩ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡ በውጭ አገር ለሚገኙ የፖለቲካ ኃይሎችም  ጥሪ ሲደረግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡ በዚሁ መሰረትም የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር መሥራችና ሊቀ መንበር  አቶ ሌንጮ ለታና የድርጅቱ  አመራሮች ሰሞኑን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ መግባት ብቻም ሳይሆን ከጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው ተደራድረዋል፡፡  በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ ሌሎች የፖለቲካ ሃይሎችም ነፍጥ ጥለው፣ ወደ አገራቸው በመግባት፣በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ሰሞኑን ጭምር መንግስት ጥሪ እያቀረበ ነው፡፡
  ለመሆኑ እነዚህ ሁሉ አዎንታዊ የፖለቲካ ለውጦች በአገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓትና የዲሞክራሲ ግንባታ ላይ ምን አስተዋጽኦ አላቸው? በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችና ፖለቲከኞች   ሂደቱን እንዴት ያዩታል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤አንጋፋ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሮ ሃሳባቸውን እንደሚከተለው አጠናቅሮታል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደር፤ ኦሎምፒያንና ጀግና ሯጭ ሻምበል ማሞ ወልዴ


  ግሩም ሠይፉ
 ከ3 ሳምንት በፊት ለዋና አሰልጣኝ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ እና ለአትሌት ሻምበል ምሩፅ ይፍጠር ማስታወሻ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ሆኖባቸው የተሰሩት ሁለት ሃውልቶች በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተተከናወነ ስነስርዓት መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የኢፌዲሪ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመተባበር ሃውልቶቹን አሰርተዋል። በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት ታሪክ ውስጥ የነበራቸው ጉልህ ድርሻና ታሪክ ለመዘከር እንደሆነም ተወስቷል። ይህን  ተከትሎ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን መካነ መቃብር የፈረሰው የሻምበል ማሞ ሐውልት መልሶ እንዲቆም በስፖርት አድማስ በኩል ጥሪ ያቀረበው የበኩር ልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ ነው፡፡  የኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ አትሌቶች አበበ ቢቂላና ማሞ ወልዴ በቅዱስ ዮሴፍ በሚገኘው መካነ መቃብር ተሰርቶላቸው የነበሩት ሐውልቶች ከ12 ዓመታት በፊት በሚያሳዝን ሁኔታ  ፈራርሰው ነበር፡፡ 

Monday, May 28, 2018

የአማራ ብሔረተኛነት ከየት ወዴት?

 

ደረጀ ይመር  
ዛሬ ዛሬ ዜጎች በሐሳብ ወይም በምክንያት ከመቀራረብ ይልቅ ለስሜት ወይም ለምንዝላታዊ መሳሳብ (primordial connection) ቅርብ ለሆነው ዘውጌ ማንነታቸው (ethnic identity) ፊት መስጠትን ይመርጣሉ፡፡ እንደ ድርና ማግ ባስተሳሰረን ኢትዮጵያዊ ማንነት ኪሳራ፣ በጥቃቅን አካባቢያዊ ሽኩቻዎች ላይ ተጠምደናል፡፡ የዘውጌ - ማንነት ጉዳይ ሁሉም  በየአቅጣጫው የሚጮኽበት አጀንዳ መሆን ከጀመረ ከራርሟል፡፡

እንደሚታወቀው በጠባብ ማንነት ዙሪያ የተደራጁ የፖለቲካ ቡድኖች በአንድ ሀገር ውስጥ በተበራከቱ ቁጥር በእዛው ልክ የእልቂት ነጋሪትን የሚጎስሙ ጽንፈኛ የዘውግ ፖለቲካ አምላኪዎች በሚያስበረግግ ደረጃ እየፋፉ ይሄዳሉ፡፡

Thursday, May 24, 2018

Democracy according to Eritrea's Afwerki, then and now

by
Isaias Afwerki is the first President of Eritrea, a position he has held since its independence in 1993 [Reuters]
Isaias Afwerki is the first President of Eritrea, a position he has held since its independence in 1993 [Reuters]

Wednesday, May 23, 2018

የኢትዮጵያ እግር ኳስና የምርጫ ጨረታ

የኢትዮጵያ እግር ኳስና የምርጫ ጨረታ
ሲንከባለል የቆየው የእግር ኳሱ ብሔራዊ ፌዴሬሽን የአመራሮች ምርጫ ለመጨረሻ ጊዜ ለግንቦት 25 ተቀጥሯል
በካምቦሎጆ ዙሪያ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የደራና የጦፈ የድለላ ሽሚያ የሚስተዋልበትን ክስተት ከመጋረጃ ጀርባ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሜቴ ምርጫ ባልተከናወነበት በዚህ ወቅት፣ ጉዳዩ ለጨረታ የቀረበ እስኪመስል የተቋሙ የዋና ጸሐፊነት ቦታና ሌሎችም በንዑስ ኮሚቴ የሚመሩ ልዩ ልዩ ክፍሎች በእነማን እንደሚመሩ ከወዲሁ ለእነማን እንደሚሆን መቃወቅ የጀመረ ይመስላል፡፡

የነ ሌንጮ መንገድ!

  መቀመጫውን በውጭ ሀገር ያደረገውና በአንጋፋዎቹ የኦሮሞ ብሄርተኞች አቶ ሌንጮ ለታ እና ዶክተር ዲማ ነገዎ የሚመራው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ከመንግሥት ጋር የፖለቲካ ድርድር መጀመሩን ካሳወቀ ጥቂት ዐመታት ተቆጥረዋል፡፡ ሆኖም ስምምነት ሊደረስ ባለመቻሉ ኦዴግ ነፍጥ ካነሳው አርበኞች ግንቦት-7 ጋር የጋራ ጥምረት እስከ መመስረት ደርሶ ነበር፡፡
                                  
የኦዴግ መሪዎች ከአንዴም ሁለቴ ወደ አዲሳባ ተመላልሰው ለኢሕኤግ-መራሹ መንግስት የድርድር ጥያቄ አቅርበውና ከሦስት ዐመታት በፊትም መለስተኛ የድርድር ሙከራ አድርገው ውጤት አላገኙበትም ነበር፡፡ በኢሕአዴግ-መራሹ መንግስት እና በሀገሪቷ አንዳንድ ፖለቲካዊ ለውጦች መከሰታቸውን ተከትሎ በቅርቡ የተደረጉ ውይይቶችና ድርድሮች ግን ፍሬ ማስገኘታቸው ሲገለጽ ሰንብቷል፡፡ ሁለቱም ወገኖች አስተማማኝ ሊባል የሚችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ይፋ አድርገዋል፡፡

ግንቦት 20 ሲመጣ የሚታወሱኝ ሁነቶች


ግንቦት 20፣ 1983 ዓ.ም አዲስ አበባ (1)




 
ግንቦት 20 ቀን ሲመጣ ሁልጊዜም የሚታወሱኝ እነዚያ በልጅነት ዘመኔ ያየኋቸው ፀጉራቸውን አንጨብርረው አፋቸው የሚያስተጋባ የኢህአዴግ ታጋዮች ናቸው። በዚያን ወቅት አያቴ “አየሁ ብያ” ትለኝና “አቤት” ስላት “ከደርግና ከኢህአዴግ ማን ይሻላል?” ብላ ትጠይቀኛለች፤ እኔ ሁለቱንም ምን እንደሆነ ለይቼ ስለማላውቅ ከአፌ የመጣልኝን እናገራለሁ፤ ታዲያ ይህን ጥያቄ በተለያየ ቀን ነው ደጋግማ የምትጠይቀኝ።


የብሔር ፖለቲካውን አደጋ እናስወግድ



 ከህሊና በላይ ፍርድን ማን ያቀናል?!
ከውቀት ሁሉ ልቆ
ከጥልቅ ስሜት ረቅቆ
በፍቅር የታነፀ
የሰላምን ብስራት
የፈጣሪን መልዕክት
ለሰው ማን ያደርሳል?!
በእውነት ከህሊና በላይ ምን አለ? ህሊና አይጨበጥም፣ አይዳሰስም፡፡ ስለመኖሩ ግን እናውቃለን - በልቦናችን ወይም በስሜታችን፡፡ ብቻ በሆነ መንገድ ህሊና እንዳለ እንረዳለን፡፡ ህሊና የፈጣሪ ፍርድ ወደኛ የሚደርስበት መንገድ ሳይሆን አይቀርም፡፡
እኔም በዛሬው ፅሁፌ፤ በህሊናዬ ለመመርመር የሞከርኩትን የአገራችን የብሔር ፖለቲካ ተዋስኦ፣ በህይወታችን ውስጥ እየተገለጠ ያለበትን ገፅታዎቹን አሳያለሁ፡፡ በፅሁፉ መጨረሻ ላይም አሁን ከገባንበት የብሔር ፖለቲካ አዙሪት ሊያስወጡን የሚችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ለመጠቆም እሞክራለሁ፡፡
በእርግጥ የአንድ ግለሰብና የአንደ ተቋም ተሞክሮ እና ምልከታ፣ የአገራችንን ገፅታ ለማሳየት በቂ ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን በተለያየ አጋጣሚ ከወዳጅ፣ ዘመድ፣ ጎረቤትና ጓደኛ እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን የምሰማቸው ተሞክሮዎች ተቀራራቢነት ከዚህ በታች የማቀርበው ትንታኔ በተወሰነ መልኩም ቢሆን የአገራችንን የብሔር ፖለቲካ ተግባራዊ ውጤት ያሳይ ይሆናል የሚል ግምትን አሳድሮብኛል፡፡
በመሆኑም ይህ ፅሁፍ የግል ተሞክሮን በመንተራስና በአጠቃላይ በአገራችን እየተከናወኑ ያሉ ሁነቶችን በመታዘብ የተዘጋጀ እንጂ የጥናት ፅሁፍ አለመሆኑን አንባቢው እንዲረዳልኝ እጠይቃለሁ፡፡

Tuesday, May 22, 2018

መንግሥቱ እና የኮሎኔል አጥናፉ ኑዛዜ









ኮ/ል መንግሥቱ ደርግን ኮትኩተው አሳድገውት ይሆናል። ነገር ግን አልወለዱትም። የደርግ እናትም አባትም ኮ/ል አጥናፉ ናቸው። ኾኖም ደርግ ፈጣሪውን መልሶ ለመብላት የወሰደበት ጊዜ ከ5 ዓመት ያነሰ ነበር፡፡ ኅዳር 3/ 1970 በዕለተ ቅዳሜ አጥናፉ ተገደሉ። "አብዮት ልጆቿን በላች" ተባለ።
ሲያልቅ አያምር ሆኖ እንጂ መንጌና አጥናፉ ጎረቤት ነበሩ። ሚስቶቻቸው ውባንቺና አስናቀች በአንድ ስኒ ቡና ጠጥተዋል። ትምህርትና ትዕግስት ከነሱራፌል አጥናፉ ጋር ኳስ ሲራገጡ፣ መሐረቤን ያያችሁ ሲጫወቱ ይውሉ ነበር። ጨርቆስ፣ መሿለኪያ፣ 4ኛ ክፍለ ጦር ግቢ የሟችም የ'ገዳይ'ም ቤት ነበር።

 መስከረም 2/1967 የአብዯት በዓል- ከግራ ወደ ቀኝ መንግሥቱ ኃይለማርያም (ሻለቃ)፣ ተፈሪ በንቲ (ብ/ጄኔራል)፣ አጥናፉ አባተ (ሻምበል)


መንጌ ቀኝ እጃቸው፣ ጎረቤታቸውና ለአጭር ጊዜም ቢሆን አለቃቸው በነበሩት ሻለቃ አጥናፉ ላይ ድንገት "ሲጨክኑ" ሐዘኑ ከባድ ሆነ። የሟች ልጅ ሱራፌል አጥናፉ እንደሚያስታውሰው ከሆነ ገራገሯ ወይዘሮ ውባንቺ ቢሻው ለቅሶ ደርሰዋቸዋል። "ትዝ ይለኛል እማዬ ወይዘሮ ዉባንቺን 'ባልሽ ባሌን ገደለው!' እያለቻት ተቃቅፈው ሲላቀሱ" ይላል ሱራፌል።
ለመሆኑ ከኮሎኔል አጥናፉ አባተ መገደል በኋላ ልጆቹ እንደምን ኖሩ? ከ8ቱ ልጆች 5ኛው ሱራፌል አጥናፉ "መንጌ አባቴን ካስገደለ በኋላ እኛን እንዳሮጌ ዕቃ ከቤት አውጥተው ጣሉን..." ሲል ረዥሙን ቤተሰባዊ ምስቅልቅ በአጭር ዐረፍተ ነገር ይጀምራል፡፡

ኢትዮጵያ እና አሳሳቢው የፊልም እንቅስቃሴዋ

በጥበቡ በለጠ

የሰው ዘር መገኛ ናት የምትባለው ኢትዮጵያ ይህን የሚያክለውን ታሪኳን ገና በደንብ አላስተዋወቀችውም፡፡ ጽላተ ሙሴ ከኔ ዘንድ ነው የምትለው ኢትዮጵያ እስካሁን ወደ አለማቀፍ ስምና ዝና አልመጣችም፡፡ ገና በሰባተኛው መቶ ክፍለ-ዘመን የእስልምና ሀይማኖት በአለም ላይ ሰፊ አድማሱን በሚያሳይበት ወቅት ኢትዮጵያ የነብዩ መሐመድ ቤተሰቦች መቀመጫ የሆነችው ኢትዮጵያ ታላቅ ፊልም አልሰራችበትም፡፡ የቅዱሳንና የታላላቅ መሪዎች ምድር የሆነችው ኢትዮጵያ ተአምራዊት ሀገር መሆንዋን በአደባባይ አላሳየችም፡፡ የጥቁር ህዝብ ሁሉ የነጻነት ተምሳሌት የሆነችው ኢትዮጵያ ታሪኳን ለጥቁሮች በሚገባ ገና አላስተማረችም፡፡ ገና ብዙ ብዙ ማስታወቂያዎች ይቀሯታል፡፡ የራስዋን ታሪክ እያጠፋች በቱርክ የፊልም ታሪኮች ተወራለች፡፡

ቁጥር 2 የአገር ህልውና አደጋ እና የ290 ሚሊዮን ብር ብክነት!


• ኢንቨስትመንትን በጠላትነት የመፈረጅና የማጥቃት ዘመቻ! ከህግ በላይ የመሆን “ልዩ መብት”!
• ስንዴና ዳቦ በተቸገረ አገር፣ የእርሻ መሬት እንዳይስፋፋ ዘመቻ የሚያካሂድ ሚኒስቴር አለን።
• ከሩብ ቢሊዮን ብር በላይ ብክነት! የ290 ሚሊዮን ብር ኪሳራ - መንግስት አለቦታው አለስራው።
^ በ675 ብር ሂሳብ፣ ስንዴ ለማቅረብ በጨረታ ያሸነፈ ኩባንያ፣ ውጤቱ በመንግስት ተሰረዘበት። ባይሰረዝ ኖሮ፣ መንግስት፣ ሁለት ሚ ኩንታል ስንዴ፣ በ1,350,000,000 ብር መግዛት ይችል ነበር።
^ በ820 ብር ሂሳብ፣ ያለጨረታ ስንዴ እንዲያቀርብ በመንግስት ተለምኖ ኩባንያው እሺ ብሏል። አሁን፣… ሁለት ሚ ኩንታል ስንዴ ለመግዛት፣ መንግስት 1,640,000,000 ብር ለመክፈል ወስኗል።

የባህርዳር ዩንቨርስቲ የግእዝ ቋንቋን ማስተማር ጀመረ


ዩንቨርስቲቅ የግዕዝ ትምህርት ክፍሉን ከከፈተበት ከየካቲት 2010 ዓ.ም ጀምሮ ከ32 በላይ ተማሪዎች በቋንቋው ለመሰልጠን ተመዝግበዋል።
የባህርዳር ዩንቨርስቲው የውጭ ግንኙነት አና ትብብር ዳይሬክተር አቶ ሞገስ አብረሀ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ለግአዝ ትምህረትና ለቋንቋው የምርምር ማእከል የሚሆን ህንጻ ለመገንባት ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የእስራኤልና ኢራን ፍጥጫ





እስራኤል የኢራን በሶሪያ መመሸግ ደስታን አይሰጣትም።ኢራን በሶሪያ ምድር የጦር ቀጣናዋን ማደራጀቷም «ሳይታሰብ ጥቃት እንድትፈፅም»ምቾት ይሰጣታል በሚል ከአካባቢው መራቋን አጥብቃ ትሻለች። የኑውክሌር መርሀ ግብሯንም ቢሆን ከበጎው ይልቅ ለክፉ አላማ የሚቀመር መሆኑን ስታምን ፕሬዚዳንት ሀሳን ሮሀኒ በአንፃሩ ይህ ፈፅሞ ከእውነት የራቀ ስለመሆኑ ይሟገታሉ።
በእርግጥም ከሁለት ዓመታት በፊት በነበረው ስምምነት መሰረት ኢራን የዩራንየም ክምችቷን መቀነስን ጨምሮ የኑውክሌር ፕሮግራሟን ለማቆም ከበለፀጉት አገራት ጋር ስምምነት ፈፅማለች።ይህ ግን ኢራን ቃሏን ስለመጠበቋ አንዳች ማረጋገጫ የለንም ለሚሉት እስራኤላውያን ፈፅሞ አይዋጥም።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሆን ስምምነቱንም ሆነ ኢራንን የሚመለከቱት በእስራኤል መነፅር ነው።በተለይ በኒውክሌር መርሃ ግብር እንደ ቤኒያሚን ኔታኒያሁ እርሳቸውም ቢሆን አያምኗትም። እናም በምርጫ ቅስቀሳቸው ቃል በገቡት መሰረት አገራቸው ከኢራን ጋር የፈረመችውን ስምምነት ለመቅደድ ብዙ ጊዜ አልጠበቁም። ከሰሞኑ ኢራን የተወሰነውን የስምምነቱን አካል እንዳላከበረች በመግለፅ ፊርማቸውን በይፋ አንስተዋል።

Remembering Nomzamo Winnie Mandela

 

 

As  her stste funeral  takes place on 14 April in Johannesburg, it is clear from the outpouring sorrow and mounting opposing views that Winnie Mandela in death – just like she was most of her life – continues to divide opinion. reGina Jane Jere reports on the life of South Africa’s enigmatic anti-apartheid heroine.

Winnie Mandela’s traditional  name Nomzano, translates to “one who strives or undergoes trials,” or, according to the urban dictionary, “mother of all endevours who does not give up, to her nothing is impossible”.
And trials, personal and political – Nomzamo Winifred Zanyiwe Madikizela-Mandela, had in abundance. But give up, she never did.

አዲስ ተስፋ የፈነጠቀው የሁለቱ ኮሪያዎች መሪዎች ግንኙነት

አዲስ ተስፋ የፈነጠቀው የሁለቱ ኮሪያዎች መሪዎች ግንኙነት
የሰሜን ኮሪያ ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡንና የደቡብ ኮሪያ አቻቸው ሙን ጃኤ-ኢን በፓንሙንጆም ድንበር የሰላም፣ የብልፅግናና የውህደት ስምምነትን ከተፈራረሙ በኋላ ተቃቅፈው ይታያሉ

 

ዓለማችን ዓርብ ሚያዚያ 19 ቀን 2010 ዓ.ም. የሰሜንና የደቡብ ኮሪያ መሪዎች የሁለቱን አገሮች ጦርነት በይፋ ለማቆም ያደረጉትን ዓይነት ስምምነት ያየችው ሁለት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ እ.ኤ.አ. በ1938 የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ኔቪል ቻምበርሌይንና የጀርመን ቻንስለር አዶልፍ ሒትለር ሲጨባበጡ፣ እ.ኤ.አ. በ1985 የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሮናልድ ሬገንና የሶቪየት ኅብረት የመጨረሻው መሪ የነበሩት ሚካኤል ጎርባቾቭ በእሳት ዙሪያ ተቀምጠው ሲነጋገሩ የታዩ ጊዜ ነበር ዓለም ተመሳሳይ ስምምነትና የሰላም ጅማሮን ያየችው፡፡
ዓለም በሶሪያና በየመን ጦርነት እየታመሰች ባለችበት በዚህ ወቅት፣ ከወደ ፓንሙንጂየም የተሰማው የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ኡንና የደቡብ ኮሪያው መሪ ሙን ጃኤ-ኢን መገናኘት ዜና ለብዙዎች ተስፋ ሰጪ የሆነ ክስተት ነበር፡፡

የኢትዮጵያ ፌዴራሊዝም ከቋንቋ ወደ ግዛታዊነት ቢሸጋገርስ?


`በክንፈ ኪሩቤል
በክፍል አንድ ሕገ መንግሥቱ ስለብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች፣ መብቶችና የፌዴራሊዝሙን ሕገ መንግሥታዊ ትርጉምና ችግሮች ተመልክተናል፡፡ በክፍል ሁለት ደግሞ በኢትዮጵያ የቋንቋ ፌዴራሊዝም መተግበር ከተጀመረ ወዲህ የታዩትን ችግሮች ተመልክተናል፡፡ በክፍል ሦስት ምን ማድረግ ይገባናል የሚል ሐሳብ እንዳስሳለን፡፡

‹‹መሥራችና ባለቤት›› እና ‹‹መጤ›› ብሔረሰቦች ግንኙት ከሕገ መንግሥቱ አንፃር

በውብሸት ሙላት
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የአገራዊ ማንነትና የአገር ግንባታ ጉዳይ ለብዙዎች አጀንዳ እየሆነ መጥቷል፡፡ ጉባዔዎች እየተካሄዱ ነው፡፡ የተወሰኑ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ለእነዚህ ጉዳዮች ትኩረት ሰጥተው በመወያየትም ላይ ይገኛሉ፡፡ የተወሰኑ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ድርጅቶችም እነዚህን ውይይቶችና የራሳቸውንም ፕሮግራም በማዘጋጀት ለሕዝብ እያስተላለፉ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ውይይቶችና ዝግጅቶች ከወትሮው በተለየ ትኩረት መሳባቸው የአገር ግንባታ ሒደቱ እንከን አጋጥሞታል የሚል ዕሳቤን መነሻ በማድረግ ይመስላል፡፡
በዚህ ጽሑፍ ካጋጠሙት ከእንከኖቹ መገለጫ ከመንስዔዎቹ ደግሞ አንዱን እንመለከታለን፡፡ አንዱ ለሌላው የመንስዔና ውጤት ግንኙነት ስለሚኖረው ነው፡፡  አገራዊ ማንነት ግንባታው ላጋጠሙት እንከኖች ማሳያ የሚሆነው ከየክልሎቹ እየተደረገ ያለው መፈናቀል ነው፡፡ የሚፈናቀሉት ደግሞ መጤ የሚባሉት ብሔሮች ናቸው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን የመጤነት ፍረጃና የማፈናቀል ተግባር የአባባሽነት ሚና ያላቸውን የክልል ሕግጋት በአስረጅነት እናነሳለን፡፡