Pages

Showing posts with label Ethiopian Affairs. Show all posts
Showing posts with label Ethiopian Affairs. Show all posts

Wednesday, May 23, 2018

ግንቦት 20 ሲመጣ የሚታወሱኝ ሁነቶች


ግንቦት 20፣ 1983 ዓ.ም አዲስ አበባ (1)




 
ግንቦት 20 ቀን ሲመጣ ሁልጊዜም የሚታወሱኝ እነዚያ በልጅነት ዘመኔ ያየኋቸው ፀጉራቸውን አንጨብርረው አፋቸው የሚያስተጋባ የኢህአዴግ ታጋዮች ናቸው። በዚያን ወቅት አያቴ “አየሁ ብያ” ትለኝና “አቤት” ስላት “ከደርግና ከኢህአዴግ ማን ይሻላል?” ብላ ትጠይቀኛለች፤ እኔ ሁለቱንም ምን እንደሆነ ለይቼ ስለማላውቅ ከአፌ የመጣልኝን እናገራለሁ፤ ታዲያ ይህን ጥያቄ በተለያየ ቀን ነው ደጋግማ የምትጠይቀኝ።


የብሔር ፖለቲካውን አደጋ እናስወግድ



 ከህሊና በላይ ፍርድን ማን ያቀናል?!
ከውቀት ሁሉ ልቆ
ከጥልቅ ስሜት ረቅቆ
በፍቅር የታነፀ
የሰላምን ብስራት
የፈጣሪን መልዕክት
ለሰው ማን ያደርሳል?!
በእውነት ከህሊና በላይ ምን አለ? ህሊና አይጨበጥም፣ አይዳሰስም፡፡ ስለመኖሩ ግን እናውቃለን - በልቦናችን ወይም በስሜታችን፡፡ ብቻ በሆነ መንገድ ህሊና እንዳለ እንረዳለን፡፡ ህሊና የፈጣሪ ፍርድ ወደኛ የሚደርስበት መንገድ ሳይሆን አይቀርም፡፡
እኔም በዛሬው ፅሁፌ፤ በህሊናዬ ለመመርመር የሞከርኩትን የአገራችን የብሔር ፖለቲካ ተዋስኦ፣ በህይወታችን ውስጥ እየተገለጠ ያለበትን ገፅታዎቹን አሳያለሁ፡፡ በፅሁፉ መጨረሻ ላይም አሁን ከገባንበት የብሔር ፖለቲካ አዙሪት ሊያስወጡን የሚችሉ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ለመጠቆም እሞክራለሁ፡፡
በእርግጥ የአንድ ግለሰብና የአንደ ተቋም ተሞክሮ እና ምልከታ፣ የአገራችንን ገፅታ ለማሳየት በቂ ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን በተለያየ አጋጣሚ ከወዳጅ፣ ዘመድ፣ ጎረቤትና ጓደኛ እንዲሁም ከመገናኛ ብዙሃን የምሰማቸው ተሞክሮዎች ተቀራራቢነት ከዚህ በታች የማቀርበው ትንታኔ በተወሰነ መልኩም ቢሆን የአገራችንን የብሔር ፖለቲካ ተግባራዊ ውጤት ያሳይ ይሆናል የሚል ግምትን አሳድሮብኛል፡፡
በመሆኑም ይህ ፅሁፍ የግል ተሞክሮን በመንተራስና በአጠቃላይ በአገራችን እየተከናወኑ ያሉ ሁነቶችን በመታዘብ የተዘጋጀ እንጂ የጥናት ፅሁፍ አለመሆኑን አንባቢው እንዲረዳልኝ እጠይቃለሁ፡፡