Pages

Saturday, June 2, 2018

ግንቦት በኢትዮጵያ ታሪክ


01 Jun 2018
በአጋጣሚም ይሁን ታስቦበት … ግንቦት በኢትዮጵያ ታሪክ በርካታ ድርጊቶች የተፈጸሙበት ወር ነው፡፡ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ታዋቂ ልጆቿን ወልዳለች፤ ወደማይቀረው ዓለምም ሸኝታለች፤ መሪዎቿን ወደ ሥልጣን አምጥታለች፤ ከሥልጣናቸው ሽራለች፤ አስከፊ ጦርነቶችን አስተናግ ዳለች፤ ከነዚህ ታሪካዊ ክስተቶች በተጨማሪ ግንቦት ያልተለመዱ ክስተቶች የተስተናገዱበት ወርም ነው፡፡ ታዲያ ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር ልዩ ቁርኝት ያለውን ይህን ወር ከመሰናበታችን በፊት ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ካስተናገደቻቸው ታሪካዊ ክስተቶች መካከል ጥቂቶቹን ብቻ በአጭሩ ለመቃኘት እንሞክር፡፡

Friday, June 1, 2018

የመጠጥ ውሃ እጥረት የኢትዮጵያ ስጋ


ኢትዮጵያ ከሰሐራ በታች ካሉ ዝቅተኛ የመጠጥ ውሃ ካላቸው አገራት አንዷ ስትሆን ለመጠጥ ውሃ ከምታመርተው ውስጥ 39 ከመቶው አገልግሎት ሳይሰጥ ይባክናል፡፡ በቀጣይም የመጠጥ ውሃ እጥረት ያጋጥማታል፡፡
ዶክተር ኢንጅነር አብዱላ ከማል በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የውሃ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ሲያብራሩ፤ በኢትዮጵያ ራሱን በዓመቱ የሚተካው የገፀ ምድር ውሃ 122 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ ነው፡፡ ተከታታይ ጥናት ባይደረግም የከርሰ ምድር ውሃው 36 ቢሊዮን ሜትር ኪዩብ እንደሆነ ይገመታል፡፡ ታዲያ በዓለም አቀፍ ስሌት አንድ ሰው በዓመት የሚያገኘው የውሃ መጠን ከ1ሺ700 እስከ 1000 ሜትር ኪዩብ ከሆነ ወደፊት የውሃ እጥረት ይኖራል ፡፡

Wednesday, May 30, 2018

አንዳርጋቸው ጽጌን በጨረፍታ

Endalegeta Kebede

.አንዳርጋቸው ጽጌ ተፈታ፤እሰይ! በኢትዮጵያ ምድር የበቀለ ሳር ቅጠሉ ሁሉ ሲናፍቀው የነበረ ዜና ነበርና የእሱ መፈታት ለፍትህ ለርትዕና ለሀገር ሲቆረቆሩ ለቆዩና መቆርቆር ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንና አፍቃሬ ኢትዮጵያውያን መልካም የምስራች ነው፡፡ አንዳርጋቸው የማይሰፈር ዋጋ ከፍሏል፡፡አይተናል፤ሰምተናል፡፡ የመፈታቱ ዜና በህይወት ላላሉት ተቃዋሚዎቹ/አሳሪዎቹ ብቻ ሳይሆን ለሞቱትም አስደንጋጭ መርዶ ሊሆንባቸው እንደሚችል ሲገመት የቆየ ነው፡፡ እንግልቱ ደግሞ በውስን ዓመታት ብቻ የሚመደብ አይደለም፡፡ ከሃያ አምስት ዓመታት በላይ በኢህአዴግ ሲወገዝ፣ አሳዳጆቹ መቆሚያ መቀመጫ ሲያሣጡት የነበረ ሰው ነው፡፡ በደርግ ዘመንም አንዲሁ፡፡
አንዳርጋቸው ጽጌን ሳስበው ‹ነጻነት› የሚለው ቃል ብሄራዊ መዝሙር ሆኖ ወደ ጆሮዬ ይገባል፡፡ አንዳንዴ ‹ነጻነት› በሚል ርዕስ የሚታወቅ፣ሁላችንም ተቀባብለን ልንዘምረው የምንመኘው ተወዳጅና ዘመን አይሽሬ ነጠላ ዜማ ያለው ሁሉ ይመስለኛል፡፡ነጻነትን በቅጡ ሳያውቁ ነጻ እናወጣለን ስለሚሉ ታጋዮች ስለጻፈ ፣እሱም ለነጻነት በሚከፈል መስዋዕትነት ከመሪ ተዋንያን መካከል አንዱ ስለሆነ እንጂ በሌላ አይደለም፡፡አሁን ተፈታ! አሁንም ምስጋና ለእነ አቢይ አህመድ(ዶክተር)ይሁን!
አንዳርጋቸው የአዲስ አበባ ልጅ ነው - አዲስ አበቤ፡፡ ከአዲስ አበባ የወጣው በ1972 ነው - በወርሃ ጥር፡፡

Tuesday, May 29, 2018

ሱስ ያደበዘዛቸው የሕይወት መስመሮች


በአፍሪካ ትልቁ ገበያ እንደሆነ በሚነገርለት በመርካቶ እንኳንስ ነጋዴው ተላልኮ የሚኖረው ምስኪን እንኳ ገንዘብ አይቸግረውም፡፡ ሌላው ቢቀር የዕለት ጉርስ ጉዳይ አያሳስበውም፡፡ የወላጆቹን የንግድ ሥራ ድርጅት ገና በልጅነቱ ለተቀላቀለው ለካሳሁን ኪሮስ ዓይነቱ ደግሞ ገንዘብ ቁም ነገሩ አይሆንም፡፡ ‹‹ብዙ ገንዘብ አገኝ ነበር፡፡ ማግኘቴን እንጂ ቆጥሬም አላውቅም፤›› ይላል ገና በ12 ዓመቱ የመርካቶን ፈጣን የንግድ እንቅስቃሴ የተቀላቀለበትን ደጉን ጊዜ ሲያስታውስ፡፡
     በንግዱም ብቻ ሳይሆን በትምህርቱም ብርቱ የነበረው ኪሮስ የስምንተኛ ክፍል ብሔራዊ የመልቀቂያ ፈተና ላይ 95 ነጥብ አስመዝግቦ ነበር ወደ ዘጠነኛ ክፍል የተዘዋወረው፡፡ በዚህ ግን ሊቀጥል አልቻለም፡፡ እንደ ልቡ የሚያገኘው ገንዘብ ከጉርምስና ጋር ተደምሮ ማንኛውንም ነገር እንዲሞክር በሕይወቱ አላስፈላጊ ቁማር እንዲጫወት መንገድ ከፈተለት፡፡ ከጓደኞቹ ጋር ሆኖ የማይወጣው ተራራ የማይወርደው ቁልቁለት አልነበረም፡፡ አደገኛ የሚባሉ ሱሶችን በተለይም መጠጥና ጫትን ይሞክርም ጀመረ፡፡

የፖለቲካ ለውጡ የፈነጠቀው ተስፋ ይኖር ይሆን?


አለማየሁ አንበሴ

• ጠ/ሚኒስትሩ የሚያነሷቸው ሀሳቦች ለሃገራዊ መግባባት ጠቃሚ ናቸው
• ሥር ነቀል የምርጫ መዋቅራዊና አስተዳደራዊ ለውጥ ያስፈልጋል
• በቅድመ ሁኔታ ላይ የታጠረ ድርድር አያስፈልግም


   የአገሪቱ የፖለቲካ ድባብ እየተለወጠ ይመስላል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ የፖለቲካ እስረኞች ተፈተዋል፡፡ አሁንም እየተፈቱ ነው፡፡ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የጠ/ሚኒስትርነት መንበሩን ከያዙ ወዲህ መንግስት የተቃዋሚ ፖለቲካ ሃይሎችን የሚመለከትበት መነጽር በእርግጥም ተለውጧል፡፡ በአገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ለሚንቀሳቀሱት ምቹ ምህዳር ለመፍጠር መንግስት ቁርጠኝነቱ እንዳለው ጠ/ሚኒስትሩ መግለጻቸው ይታወቃል፡፡ በውጭ አገር ለሚገኙ የፖለቲካ ኃይሎችም  ጥሪ ሲደረግ መቆየቱ አይዘነጋም፡፡ በዚሁ መሰረትም የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር መሥራችና ሊቀ መንበር  አቶ ሌንጮ ለታና የድርጅቱ  አመራሮች ሰሞኑን አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ መግባት ብቻም ሳይሆን ከጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ጋር ተገናኝተው ተደራድረዋል፡፡  በትጥቅ ትግል ላይ ያሉ ሌሎች የፖለቲካ ሃይሎችም ነፍጥ ጥለው፣ ወደ አገራቸው በመግባት፣በሰላማዊ መንገድ የፖለቲካዊ ትግላቸውን እንዲቀጥሉ ሰሞኑን ጭምር መንግስት ጥሪ እያቀረበ ነው፡፡
  ለመሆኑ እነዚህ ሁሉ አዎንታዊ የፖለቲካ ለውጦች በአገሪቱ የፖለቲካ ሥርዓትና የዲሞክራሲ ግንባታ ላይ ምን አስተዋጽኦ አላቸው? በአገር ውስጥ ያሉ ተቃዋሚዎችና ፖለቲከኞች   ሂደቱን እንዴት ያዩታል? የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤አንጋፋ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግሮ ሃሳባቸውን እንደሚከተለው አጠናቅሮታል፡፡

የኢትዮጵያ ወታደር፤ ኦሎምፒያንና ጀግና ሯጭ ሻምበል ማሞ ወልዴ


  ግሩም ሠይፉ
 ከ3 ሳምንት በፊት ለዋና አሰልጣኝ ዶክተር ወልደመስቀል ኮስትሬ እና ለአትሌት ሻምበል ምሩፅ ይፍጠር ማስታወሻ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ ሆኖባቸው የተሰሩት ሁለት ሃውልቶች በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በተተከናወነ ስነስርዓት መመረቃቸው ይታወሳል፡፡ የኢፌዲሪ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር፤ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን እና የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በመተባበር ሃውልቶቹን አሰርተዋል። በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ስፖርት ታሪክ ውስጥ የነበራቸው ጉልህ ድርሻና ታሪክ ለመዘከር እንደሆነም ተወስቷል። ይህን  ተከትሎ ጎተራ አካባቢ በሚገኘው የቅዱስ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያን መካነ መቃብር የፈረሰው የሻምበል ማሞ ሐውልት መልሶ እንዲቆም በስፖርት አድማስ በኩል ጥሪ ያቀረበው የበኩር ልጁ ሳሙኤል ማሞ ወልዴ ነው፡፡  የኢትዮጵያ ፈር ቀዳጅ አትሌቶች አበበ ቢቂላና ማሞ ወልዴ በቅዱስ ዮሴፍ በሚገኘው መካነ መቃብር ተሰርቶላቸው የነበሩት ሐውልቶች ከ12 ዓመታት በፊት በሚያሳዝን ሁኔታ  ፈራርሰው ነበር፡፡ 

Monday, May 28, 2018

የአማራ ብሔረተኛነት ከየት ወዴት?

 

ደረጀ ይመር  
ዛሬ ዛሬ ዜጎች በሐሳብ ወይም በምክንያት ከመቀራረብ ይልቅ ለስሜት ወይም ለምንዝላታዊ መሳሳብ (primordial connection) ቅርብ ለሆነው ዘውጌ ማንነታቸው (ethnic identity) ፊት መስጠትን ይመርጣሉ፡፡ እንደ ድርና ማግ ባስተሳሰረን ኢትዮጵያዊ ማንነት ኪሳራ፣ በጥቃቅን አካባቢያዊ ሽኩቻዎች ላይ ተጠምደናል፡፡ የዘውጌ - ማንነት ጉዳይ ሁሉም  በየአቅጣጫው የሚጮኽበት አጀንዳ መሆን ከጀመረ ከራርሟል፡፡

እንደሚታወቀው በጠባብ ማንነት ዙሪያ የተደራጁ የፖለቲካ ቡድኖች በአንድ ሀገር ውስጥ በተበራከቱ ቁጥር በእዛው ልክ የእልቂት ነጋሪትን የሚጎስሙ ጽንፈኛ የዘውግ ፖለቲካ አምላኪዎች በሚያስበረግግ ደረጃ እየፋፉ ይሄዳሉ፡፡

Thursday, May 24, 2018

Democracy according to Eritrea's Afwerki, then and now

by
Isaias Afwerki is the first President of Eritrea, a position he has held since its independence in 1993 [Reuters]
Isaias Afwerki is the first President of Eritrea, a position he has held since its independence in 1993 [Reuters]

Wednesday, May 23, 2018

የኢትዮጵያ እግር ኳስና የምርጫ ጨረታ

የኢትዮጵያ እግር ኳስና የምርጫ ጨረታ
ሲንከባለል የቆየው የእግር ኳሱ ብሔራዊ ፌዴሬሽን የአመራሮች ምርጫ ለመጨረሻ ጊዜ ለግንቦት 25 ተቀጥሯል
በካምቦሎጆ ዙሪያ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የደራና የጦፈ የድለላ ሽሚያ የሚስተዋልበትን ክስተት ከመጋረጃ ጀርባ እያስተናገደ ይገኛል፡፡ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሜቴ ምርጫ ባልተከናወነበት በዚህ ወቅት፣ ጉዳዩ ለጨረታ የቀረበ እስኪመስል የተቋሙ የዋና ጸሐፊነት ቦታና ሌሎችም በንዑስ ኮሚቴ የሚመሩ ልዩ ልዩ ክፍሎች በእነማን እንደሚመሩ ከወዲሁ ለእነማን እንደሚሆን መቃወቅ የጀመረ ይመስላል፡፡

የነ ሌንጮ መንገድ!

  መቀመጫውን በውጭ ሀገር ያደረገውና በአንጋፋዎቹ የኦሮሞ ብሄርተኞች አቶ ሌንጮ ለታ እና ዶክተር ዲማ ነገዎ የሚመራው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ከመንግሥት ጋር የፖለቲካ ድርድር መጀመሩን ካሳወቀ ጥቂት ዐመታት ተቆጥረዋል፡፡ ሆኖም ስምምነት ሊደረስ ባለመቻሉ ኦዴግ ነፍጥ ካነሳው አርበኞች ግንቦት-7 ጋር የጋራ ጥምረት እስከ መመስረት ደርሶ ነበር፡፡
                                  
የኦዴግ መሪዎች ከአንዴም ሁለቴ ወደ አዲሳባ ተመላልሰው ለኢሕኤግ-መራሹ መንግስት የድርድር ጥያቄ አቅርበውና ከሦስት ዐመታት በፊትም መለስተኛ የድርድር ሙከራ አድርገው ውጤት አላገኙበትም ነበር፡፡ በኢሕአዴግ-መራሹ መንግስት እና በሀገሪቷ አንዳንድ ፖለቲካዊ ለውጦች መከሰታቸውን ተከትሎ በቅርቡ የተደረጉ ውይይቶችና ድርድሮች ግን ፍሬ ማስገኘታቸው ሲገለጽ ሰንብቷል፡፡ ሁለቱም ወገኖች አስተማማኝ ሊባል የሚችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ይፋ አድርገዋል፡፡